Home News ለቸኮለ! የዛሬ ማክሰኞ ታህሳስ 30/2011 አበይት ዜናዎች- ከዋዜማ ራዲዮ

ለቸኮለ! የዛሬ ማክሰኞ ታህሳስ 30/2011 አበይት ዜናዎች- ከዋዜማ ራዲዮ

by AddisDaily
6 comments

ለቸኮለ! የዛሬ ማክሰኞ ታህሳስ 30/2011 አበይት ዜናዎች- ከዋዜማ ራዲዮ

1. ጦር ሃይሉን እንደገና የባሕር ሃይል ባለቤት ለማድረግ አንዳንድ ሥራዎች መጀመራቸውን የመከላከያ ሚንስትር አይሻ መሐመድ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተናግረዋል፡፡ ለዚህም ከኬንያ እና ፈረንሳይ የባህር ሃይል አደረጃጀት ልምዶች ተወስደዋል፡፡ ባለፉት ጥቂት ወራት አስፈላጊ ፈተናዎችን ማለፍ ያልቻሉ ከ7 ሺህ በላይ የሚሆኑ የሠራዊቱ አባላት በጡረታ ተገልለዋል፡፡ ሚንስትሯ ዛሬ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት የመንፈቅ ሪፖርት ሠራዊቱ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በግጭት ሳቢያ የተፈናቀሉ ወገኖችን ወደ ቀያቸው መልሶ እያቋቋመ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

2. ሳዑዲ የኢትዮጵያዊያን ቤት ሠራተኞችን መነሻ ደመወዝ 1 ሺህ ሪያል ለማድረግ ተስማምታለች፡፡ ደመወዝ ወለሉ ከፍ ያለው የማሕበራዊ ጉዳይ ሚንስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ ከሳዑዲ አቻቸው ጋር ታህሳስ 28 ቀደም ሲል የተፈረመውን የሠራተኛ ስምምነት ውል አፈጻጸም አስመልክተው በደረሱት መግባባት መሠረት መሆኑን የመንግሥት መገናኛ ብዙኻን ዘግበዋል፡፡ የሠራተኞች መብት ስለሚጠበቅበት ሁኔታም መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ የውሉን አተገባበር በየ6 ወሩ የሚገመግም የጋራ የባለሙያዎች ቡድንም ይቋቋማል፡፡

3. ተቀማጭነቱ የተባበሩት ኢምሬቶች የሆነው “አል ማክቱም” ፋውንዴሽን በአዲስ አበባ ለአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ተናጋሪ ተማሪዎች ጋራ ጉሪ የሚል ስያሜ የተሰጠው ትምህርት ቤት መክፈቱን አዲስ ስታንዳርድ አስነብቧል፡፡ ትምህርት ቤቱ የተከፈተው የካ ክፍል ከተማ ውስጥ ሲሆን ከ5ኛ እስከ 9ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ያስተምራል፡፡ ለመጭዎቹ 5 ዐመታት የመምህራንን ደመወዝ ፋውንዴሽኑ ይሸፍናል፡፡ ከሚቀጥለው ዐመት ጀምሮ ደሞ ጎበዝ ተማሪዎች ነጻ የውጪ ትምህርት ዕድል እንዲያገኙ እንደሚያደርግ የአዲስ አበባ መስተዳድር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ታቦር ገብረ መድኅን ተናግረዋል፡፡

4. የጉጂ ኦሮሞ አባ ገዳዎች መቻቻልን እና ሰላምን ለመስበክ ያንድ ሳምንት የሰላም አዋጅ አውጀናል ብለዋል፡፡ አዋጁ ከትናንት ጀምሮ እስከ መጭው ዕሁድ ይቆያል፡፡ በሳምንቱ ሰላም እና መቻቻልን የሚያጠናክሩ የተለያዩ የውይይት መርሃ ግብሮች ይኖራሉ፡፡

5. በደቡብ ክልል የሚገኘው አባያ ሐይቅ በእንቦጭ አረም መጠቃቱን የጋሞ ዞን አካባቢ ጥበቃና ደን ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ ኢዜአ እንደዘገበው እንቦጭ በሐይቁ ላይ መታየት የጀመረው በ2009 ዓ.ም ሲሆን ባሁኑ ሰዓት 2000 ሄክታር ያህል የሐይቁ ክፍል በአረሙ ተሸፍኗል፡፡ ካሁን ቀደም 10 ሺህ ሕዝብ በማስተባበር 30 ሄክታር ለማጽት ተችሎ ነበር፡፡

ለሌሎች ያጋሩ SHARE SHARE SHARE

Source: Wazema Radio ዋዜማ ሬዲዮ Facebook

You may also like

6 comments

Zerakumsa Kebu Chabo January 8, 2019 - 9:32 am

ምነው ሁላችን ብንማርበት በአም አቀፍ ወይም አገር አቀፍ ቋንን ቢያደርጉት
=============*========*===========
ተቀማጭነቱ የተባበሩት ኢምሬቶች የሆነው “አል ማክቱም” ፋውንዴሽን በአዲስ አበባ ለአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ተናጋሪ ተማሪዎች ጋራ ጉሪ የሚል ስያሜ የተሰጠው ትምህርት ቤት መክፈቱን አዲስ ስታንዳርድ አስነብቧል፡፡ ትምህርት ቤቱ የተከፈተው የካ ክፍል ከተማ ውስጥ ሲሆን ከ5ኛ እስከ 9ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ያስተምራል፡፡ ለመጭዎቹ 5 ዐመታት የመምህራንን ደመወዝ ፋውንዴሽኑ ይሸፍናል፡፡ ከሚቀጥለው ዐመት ጀምሮ ደሞ ጎበዝ ተማሪዎች ነጻ ትምህርት ዕድል እንዲያገኙ እንደሚያደርግ የአዲስ አበባ መስተዳድር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ታቦር ገብረ መድኅን ተናግረዋል፡፡

Yihenew Alebet January 8, 2019 - 9:33 am

Thankyou

u1218u12edu1233u12cd u12abu1233 January 8, 2019 - 9:44 am

ኦሮምኛ የሀገራችን ብሔራዊ ቋንቋ ቢሆን ለኢትዮጵያ ሰላም የጎላ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

Ayenew Kasahun January 8, 2019 - 9:50 am

ይድረስ ለአለምነህ በዚህ ዜና ተራ ቁጥር 4 ጉጅ የሚለው ጉጂ በሚል ቢስተካከል ።

Yohannes Hailemeskel January 8, 2019 - 10:00 am

ባህር ሃይል በክራይ ባህር ይቻላል እንዴ? የባህር ክራይ ክፍያ ቀን ሲያልፍ መርከቡን ጫት መቃሚያ እና ባህር ኃሎቻችን ካዳሚያቸው ነው ሚሆኑት? ተው እንጂ አታስቁን አታሳቁን በሏቸው

Semeru Yimer Yimer January 8, 2019 - 10:04 am

Tnx!

Comments are closed.

About Us

AddisDaily is an Ethiopian News and related topics provider website.  Find our daily updated Ethiopian News on our YouTube channel. @Addis_Daily

 

©2025 AddisDaily.com, A Digital Media Company – All Rights Reserved. Designed and Developed by AddisSolultions.com