የካቲት12 ሲታወስ
የካቲት 12 ሲመጣ ጣልያን ኢትዮጵያን በወረችበት ጊዜ በጀነራል ግራዝያኒ አዛዥነት በሦስት ቀናት ውስጥ ብቻ 30 ሺህ ዜጎች መጨፍጨፋቸውን ታሪክ ይዘክራል።
ኢጣሊያ ንጉሣዊ ቤተሰብ አንድ ልዑል በመወለዱ ምክንያት በጄነራል ግራዚያኒ ትዕዛዝ በቀድሞው የገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቅጽር ግቢ ከተሰበሰቡት የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፤ ለፋሺስቶቹ ያደሩ ከሀዲ ባንዳዎችና መኳንንት፤ የፋሺስት ባለ ሥልጣናት ወታደሮች በተሰበሰቡበት መኻል፣ አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም የእጅ ቦምብ ወርውረው አደጋ ሲጥሉ ግራዚያኒን ጨምሮ ብዙ ሰዎች ተጎድተዋል። ይኸንን ድርጊት በመበቀል ሰበብ እዚያው ግቢ ውስጥ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ተጨፈጨፉ፤ ቀጥሎም የተማሩ ወጣቶች፣ የጦር መኮንኖችና ካህናት፣ የደብረ ሊባኖስ መነኮሳት በሙሉ እየተለቀሙ ተጨፈጨፉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በቤት ውስጥ እያስገቡ ከውጭ ቆልፈው ቤንዚን እያርከፈከፉ አቃጠሉአቸው። በአካፋ፣ በዶማ፣ በመጥረቢያ በተገኙበት ኢትዮጵያውያንን እየቆራረጡ የደም ጎርፍ አወረዱ። ፋሽስቶች የአዲስ አበባንና የአካባቢውን ሕዝብ በጅምላ ጨፈጨፉት። በሶስት ቀናት ፴ሺህ ሕዝብ መስዋዕትነት ተቀበለ።
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ምላሽ ሰጡ | የካቲት 12 የሰማዕታት | Remembering Yekatit 12 Addis Ababa Massacre | #Ethiopia #yekatit12
Watch daily updated Ethiopian news from a reliable and balanced source. Addis Media is an independent Ethiopian-related News and other programs, producer.
Visit us https://AddisMedia.net Subscribe to our channel to follow everything related to Ethiopia
Subscribe to Addis Media YouTube channel for daily Ethiopian News
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ምላሽ ሰጡ | የካቲት 12 የሰማዕታት ቀን | Remembering Yekatit 12 Addis Ababa Massacre | #Ethiopia
0