ለቸኮለ! የዛሬ ረቡዕ ታህሳስ 24/2011 አበይት ዜናዎች- ከዋዜማ ራዲዮ
1. ንጉሡ ጥላሁን የጠቅላይ ሚንስትሩ ፕሬስ ሴክሬታሪ ሃላፊ ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚንስትር ጸህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ ሴክሬታሪ ቢልለኔ ስዩም እና ምክትላቸው ሄለን ዮሴፍ ዛሬ ከሃላፊነት ተነስተዋል ሲል ፋና ዘግቧል፡፡ በሄለን ምትክ ደሞ ካሳሁን ጎፌ ተተክተዋል፡፡ ንጉሡ ቀደም ሲል የአማራ ክልል ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን ባሁኑ ሰዓት ደሞ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ናቸው፡፡ የኦዴፓው ካሳሁን ደሞ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚንስትር ደዔታ ሆነው አገልለዋል፡፡ አዲስ ስታንዳርድ አመሻሹን ባስነበበው ዘገባ ግን ቢልለኔ ስዩምና ሄለን ዮሴፍ በሀላፊነታቸው ይቀጥላሉ፣ አቶ ንጉሡ የፕሬስ ፅህፈት ቤቱ ሀለፊ መሆን የቀሪዎቹን የስልጣን ድርሻ አይነካም ብሏል። የካሳሁን ጎፌ ሹመትንም ሀሰት ነው ብሏል ዘገባው።
2. የቻይናው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዋንግ ይ ዛሬ አዲስ አበባ ይገባሉ፡፡ በ3 ቀናት ቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ከአቻቸው ወርቅነህ ገበየሁና ከአፍሪካ ኅብረት ባለሥልጣናት ጋር ይወያያሉ፡፡ በመቀጠልም ለተመሳሳይ ጉብኝት ወደ ቡርኪና ፋሶ፣ ሴኔጋል እና ጋምቢያ ያደርጋሉ፡፡
3. በአማራ ክልል በኮማንደር ውበቱ ሽፈራው ቤት ውስጥ የተያዙትን ሕገ ወጥ ሽጉጦች ወደተለያዩ ቦታዎች ለማሰራጨት ታቅዶ እንደነበር የክልሉ ሰላምና ደኅንነት ቢሮ ሃላፊ ተናግረዋል፡፡ ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ለDW እንዳሉት ሽጉጦቹ አዲስ እና ቱርክ ሰራሽ ናቸው፡፡ ወንጀሉ ባንድ ሰው ብቻ የተፈጸመ አይመስለንም፤ ተባባሪዎች እንደሚኖሩ ስለምንጠረጥር ክትትል እያደረግን ነው ብለዋል፡፡ ተጠርጣሪው የክልሉ ልዩ ጥበቃ ፖሊስ አዛዥ ናቸው፡፡
4. በደቡብ ክልል ካፋ ዞን፣ ደቻ ወረዳ ባለፈው ቅዳሜ 9 ሰዎች በድንገተኛ ጥቃት ተገድለዋል፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው ባንድ ሠፈራ ጣቢያ ውስጥ መሆኑን ሪፖርተር የአካባቢውን ምንጮች ጠቅሶ አስነብቧል፡፡ በጥቃቱ ሌሎች 4 ሰዎች ክፉኛ ተጎድተዋል፤ ብዙ ንብረትም ወድሟል፡፡ ጥቃት አድራሾቹ ከዞኑ ጠረፋማ አካባቢዎች ወይም ከአጎራባቾቹ ቤንች ማጂና ደቡብ ኦሞ ዞኖች የመጡ መዔኒት የተባሉ አርብቶ አደር ጎሳ አባላት እንደሆኑ ተገምቷል፡፡
5. መንግሥት መጭውን የገና በዐል በማስመልከት ለ530 ታራሚዎች ይቅርታ አድርጓል፡፡ በተለይ ሕጻናት ልጆች ያሏቸው ሴት ፍርደኞች ቅድሚያ ተሰጥቷቸዋል- ብለዋል የጠቅላይ ዐቃቤ ሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ ዝናቡ ቱኑ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፡፡ የይቅርታው ተጠቃሚዎች በዐቃቤ ሕግ ስር በፌደራልና ክልል ወህኒ ቤቶች የሚገኙ ታራሚዎች ናቸው፡፡ ባለፈው ዐመት የምህረት አዋጅ ሥራ ላይ ከዋለ ወዲህ ከ13 ሺህ በላይ ሰዎች ምህረት አግኝተዋል፡፡
በሌላ ዜና ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በቡራዩ ጥቃት እንደተሳተፉ በጠረጠራቸው 109 ግለሰቦች ላይ ዛሬ ክስ መመስረቱን ተናግሯል፡፡ ከእነዚህ መካከል 28 በሌሉበት ክስ የተመሠረተባቸው ናቸው፡፡
6. በታንዛኒያ 14 ኢትዮጵያዊያን መኪና ውስጥ ተፋፍገው መሞታቸው ተነግሯል፡፡ ሟቾቹ በዛምቢያ ወይም በማላዊ በኩል አቋርጠው ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ያለሙ ስደተኞች ሊሆኑ እንደሚችሉ የሀገሪቱ ፖሊስ ገልጧል፡፡
7. ሱዳን ውስጥ ሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ያገቷቸው 16 ኢትዮጵያዊያን ተለቀዋል፡፡ ታጋች ስደተኞቹ የተለቀቁት የሱዳን ጸጥታ ሃይሎች በወሰዱት የሃይል ርምጃ መሆኑን ሸገር ዘግቧል፡፡ አሁን በካርቱም የኢትዮጵያዊያን ማኅበረሰብ መጠለያ ውስጥ ይገኛሉ፡፡
ለሌሎች ያጋሩ SHARE SHARE
Source: Wazema Radio ዋዜማ ሬዲዮ Facebook
13 comments
Tnx!
ዋዜማችን የኛ የመረጃ ምንጫችን እናመሰግናለን
ቢልለኔ ፍጹም ሳይሆን ቢልለኔ ሥዩም ነው።
Thank you so much, dears!
Really information source wazema
በከፋ ዞን የሞቱት ከከምባታ ጠምባሮ ዞን የሄዱ ሰፋርዎች ስሆኑ ፈራሹ ክልል ደቡብ እና አዉሬዉ ፓርት ደኢህዴን መጠበቅም ሆነ የሀዘን መግለጫ መዉጣት አለመቻሉ አሰዝኖናል። ለማን አቤት ይባል ይሆን?
ደቡብ።ክልል።ከፈ።ዞን።ደኘ።ወረደ።9ሰዎች።በምን።አደገነዉ።የጎችሁ
አቶ ንጉሡ ጥላሁን በሚል ይስተካከል ሌላ ጣጣ አታምጡብን ??
እናመሰግናለን
thank u but stop using the word ደሞ instad of ደግሞ
Thankyou
Thanks
ከያቺ ነገር ቀጥሎ ሱሴ ዋዜማዎች ሆናችዋል። ፈጣን፦ ተደራሽ፦ ትኩስና ወቅታዊ መረጃ ለሰፊዉ ማ/ሰብ ተጨንቃችሁና ተጠባችሁ ለምታደርሱን መረጃ ከልቤ አመሰግናለዉ!!!
Comments are closed.